የትውልድ ሀገሬ

አዶላ ልበልሽ ወይስ ክብረ መንግስት

መልካሟ ከተማ ፡ የወርቛ እመቤት

የሻኪሶውን ወርቅ፡ የያዘው ከርስሽ

ክብረመንግስት የሚል : ስም ነው ያስጠሽ

በእውነት ለአገር አንቺ ክብር ነሽ

ወርቅ በያይነቱ ፡ አምርተሽ ሰጥተሽ

እንደው ክብረ መንግስት ፡ አንቺስ ደህና ነሽ?

የአንፈራራን ዳገት ፡ ቁልቁለት ወርጄ

መቼ ነው የማይሽ፡ ወዳአንቺ መጥቼ

የጥጋቡ ዘመን ፡ የቅቤ ወተቱ

እንደምን ይረሳል፡ አዮ ፋዲ ኮቱ

ግንቦት ሰኔ ደርሶ፡ የምንበለው እሸት

ናፍቆቱ መጣብኝ ፡ ትዝ አለኝ በድንገት

በአይነ ህሊናዬ፡ አውጥቼ አውርጄ

በቆየ ትዝታ ፡ በናፍቆት ነጉጄ

በሃገሬ አለማደግ፡ እጅግ ተናድጄ

ማህድኗ ብዙ ፡ እሷ ምስኪን ደሀ

ወርቅ እያፈሰስች እንደወራጅ ውሃ

ክብረ መንግስት ምነው፡ እያደር ማነሷ

ፈጥና እንድትለወጥ ፡ እንድትበለጽግ

ምን ይሆን ብልሃቱ፡ አዶላ እንድታድግ